ያለፉትን ዓመታት በሴርያው የነገሱት ጁቬንቱስ ዘንድሮ ላይ ውጤት ሲርቃቸው በ ኤሲ ሚላን ሽንፈት አስተናግደዋል ።
• ብራሂም ዲያዝ ፣ ሬቢች እና ቶሞሪ በወሳኙ መርሐ ግብር ኤሲ ሚላንን አሸናፊ ያደረገች ግብ ከመረብ ማሳረፍ የቻሉ ተጫዋቾች ናቸው ።
• ዝላታን ኢብራሂሞቪች በጨዋታው ባጋጠመው ጉዳት ተቀይሮ ወጥቷል ።
• ሚላን ከሜዳቸው ውጪ ጁቬንቱስን ሲያሸንፉ ከ አስር ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ።
• ውጤቱን ተከትሎ ጁቬንቱስ የአውሮፓ መድረክ ተሳትፏቸው አጣብቂኝ ውስጥ ሲገባ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል ።
• ወሳኙን ሶስት ነጥብ ያሳኩት ሚላኖች በተቃራኒው በሶስት ነጥብ ርቀው ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ ።