ለማግኘት በጣም ከባድና ውድ የተባለ አንድ ሐምራዊ አልማዝ ክብረ ወሰን በሚባል ዋጋ ተሸጠ። ይህ አልማዝ የተሸጠው በጨረታ ሲሆን ጨረታው ስዊዘርላንድ አገር ነው የተካሄደው።
14.8 ካራት የሚመዝነው ይህ አልማዝ “ዘ ስፕሪት ኦፍ ሮዝ” የሚል ስም ተሰጥቶታል። እስከዛሬም ለጨረታ ከቀረቡ አልማዞች ትልቁ ነው።
99 ከመቶ የሚሆኑ የሐምራዊ ሮዛማ ቅይጥ ቀለም ያላቸው አልማዞች የካራት መጠን ከ10 በታች እንጂ 14 ካራት አይደርሱም።ይህን አልማዝ ልዩ የሚያደርገውም መጠኑና የቀለም ስብጥሩ ነው ተብሏል።ይህን ውድ አልማዝ በጨረታ አሸንፎ የገዛው ግለሰብ ማንነት ይፋ አልተደረገም።