Home Entertainment News የታይዋን ፓርላማ አባላት የአሳማ ስጋ በመወርወር ተቃውሟቸውን ገለፁ

የታይዋን ፓርላማ አባላት የአሳማ ስጋ በመወርወር ተቃውሟቸውን ገለፁ

by sam

ከአሜሪካ የሚገባው የአሳማ ስጋ ምርት ጋር የተያያዘው መመሪያ ቀለል ብሏል በሚልም ነው ፓርላማው ውስጥ ይህ የተፈጠረው።

በቅርቡም የታይዋን መንግሥት ከአሜሪካ እንዲገባ የፈቀደው የአሳማ ስጋ ራክቶፓሚን የሚባል ሱስ የሚያስይዝና በታይዋንና በአውሮፓ ህብረት የታገደ ንጥረ ነገር የያዘ ነው ተብሏል። ንጥረ ነገሩ ለጤና ስጋትም እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ታይዋንም ለአሳማ ስጋዎች ጥቅም ላይ እንዳይውል ከልክላዋለች።

ገዢው ፓርቲው በበኩሉ ይህን ክስ ያስተባበለ ሲሆን ምክንያታዊ ወደሆኑ ንግግሮችም እንዲመለሱ ጠይቋል።

እንዲህ አይነት ቁጣዎችና ድብድቦች ለታይዋን ፓርላማ አዲስ አይደሉም።

የታይዋን ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ ኩዎሚንታ (ኬኤምቲ) ፓርቲ የአሳማ አንጀትና ስጋ በባልዲ ይዘው ወደ ፓርላማ በማምጣትና በመወርወር ጠቅላይ ሚኒስትር ሱ ሴንግ ቻንግ ጥያቄና መልስ እንዳያካሂዱም ለማድረግ ሞክረዋል።

የአሳማ አንጀት መወርወር ብቻ ሳይሆን በተቃዋሚው ፓርቲ ኬኤምቲና ቼን ፖ ዌይ በተባለው ፓርቲ አባላት መካከልም ቡጢ እንደተሰነዘረም ሮይተርስ የዜና ወኪል አስነብቧል።

Leave a Comment

Related Posts

en_USEnglish