የተራራው እርዝመት ከዚህ ቀደም ከተመዘገበበት በአንድ ሜትር በሚጠጋ ብልጫ ማደጉንም የኔፓልና የቻይና ባለስልጣናት አሳውቀዋል።
አገራቱ በተራራው እርዝመትም ተስማምተው የማያውቁ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን ሁለቱም 8 ሺህ 848̇.86 ሜትር እርዝማኔ አለው ብለዋል።
ቻይና ከዚህ ቀደም በልኬቴ መሰረት 8 ሺህ 8444.43 ሜትር ነው ስትል የነበረ ሲሆን ይህም ኔፓል ለካሁት ከምትለው በአራት ሜትር ያንስ ነበር።
ኤቨረስት ተራራ በቻይናና በኔፓል መካከል የሚገኝ ሲሆን በሁለቱም አገራት በኩል ተራራውንም መውጣት ይቻላል።