ትዊተር የተሰኘው ማሕበራዊ ድር አምባ ፈጣሪ የሆነው ጃክ ዶርዚ የመጀመሪያ ትዊት በ2.9 ሚሊዮን ዶላር [117 ሚሊዮን ብር ገደማ] ተሸጠ።
ትዊቱን የገዛው ማሌዢያ ውስጥ የሚገኝ አንድ ሃብታም እንደሆነ ተጠቁሟል።
የመጀመሪያው መልዕክት “ትዊተሬን እያዘጋጀሁ እገኛለሁ” የሚል ሲሆን የተለጠፈው በፈረንጆቹ መጋቢት 21/2006 ነበር።
ዶርዚ ይህንን ትዊት ለጨረታ ያቀረበው ገቢውን ለእርዳታ ለማዋል በማሰብ ነው።
መቀመጫውን ማሌዢያ ያደረገው ገዥ ሲና ኤስታቪ ትዊቱን መግዛት ማለት የሞና ሊዛን ስዕል እንደመግዛት ነው ብሏል