Gall-up የተባለው ድርጅት ባደርገው ጥናት መሰረት በአለማችን ላይ አንደኛ ደስተኛ አገር ተብላ የተሰየመቸው ፊንላንድ ነች፡፡ ፊንላንድ በአውሮፓ ውስጥ የምትገኝ ስትሆን በሁለተኛ እና በሶስተኛ ደረጃ የአለማችን ደሰተኛ አገሮች አይስላንድ እና ዴንማርክ ሆነው ተገኝተዋል፡፡
ጥናቱ የተካሄደው በሃብት ብዛት ላይ በማትኮር ሲሆን ሰዎች ከሌሎች ሰዎች ጋር ያላቸው ቅርብ ግንኙነትና መልካም አስተሳሰብ በተለያዩ ጥያቄዎች በመካተት እንደሆነ ታውቋል፡፡ በአለማችን ላይ ከሚገኙ አገሮች የመጨረሻ ደስተኛ ያልሆነች የተባለችው አገር ደግሞ አርጀንቲና ሆና ተገኝታለች፡፡