ሙዚቀኛዋና ተራማጅ የፋሽን ኢንዱስትሪ ባለድርሻዋ ሪሃና በይፋ የቢሊየነሮች መዝገብ ላይ ስሟ መስፈር ችሏል።
ፎርብስ የተሰኘው የልጥጥ ሃብታሞችን የባንክ ደብተር የሚያወዳድር መፅሔት፤ ሪሃን በዓለማችን ካሉ ቱጃር ሴት ሙዚቀኞች አንዷ ሆናለች ብሏል።
የፖፕ ሙዚቃ ኮከቧ ሪሃና 1.7 ቢሊዮን ዶላር አላት፤ ከዚህ መካከል 1.4 ቢሊዮን ዶላሩ የመጣው ፌንቲ ከሚባለው የመዋቢያ ምርቶች ፈብራኪ ድርጅቷ ነው ብሏል ፎርብስ።
ይህ ዶላር አሁን ባለው የውጭ ምንዛሪ ቢመታ ወደ 76 ቢሊዮን ብር ሊመነዘር ይችላል።
የሪሃና የተቀረ ሃብት የሚመጣው ሳቬጅ ኤክስ ፌንቲ ብላ ከሰየመችው የውስጥ ልብስ መሸጫ ሱቋ ነው።
ከዚህ ከምታገኘው ዶላር በተጨማሪ ከሙዚቃና ከትወና የምታገኘውም የሚናቅ አይደለም ይላል መፅሔቱ።