ትዊተር ሠራተኞቹን ‘ከናካቴው ቢሮ አትምጡ’ አለ
ዋና መሥሪያ ቤቱን ሳን ፍራንሲስኮ ያደረገው ትዊተር፤ አምስት ሺህ ተቀጣሪዎች ያሉት ሲሆን፤ ላለፉት ሁለት ወራት ከቤት ሲሠሩ ነበር። ተቀጣሪዎቹ ከቤት መሥራታቸው ፍሬያማ መሆኑን ያስተዋለው ትዊተር፤ ከዚህ በኋላ ሠራተኞቹ ወደ ቢሮ መሄድ እንደማይጠበቅባቸው አስታውቋል። ከቤት ሥሩ የተባሉት ተቀጣሪዎች፤ የሥራ መደባቸው ከቢሮ ውጪ እንዲሠሩ የሚፈቅድላቸው ናቸው።