የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች በትንንሽ ቡድኖች ልምምድ ሊጀምሩ ነው
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊጉ እግር ኳስ ቡድኖች ተጫዋቾች በአነስተኛ ቡድን እየሆኑ ከማክሰኞ ጀምሮ ልምምድ መሥራት እንዲጀምሩ ስምምነት ላይ ደረሱ። ሊጉ ከመጋቢት ወር ጀምሮ የተቋረጠ ሲሆን ተጨዋቾችም ብቻቸውን ብቻ ልምምድ ሲያደርጉ ቆይተው ነበር። አሁን ግን ወደ ልምምድ ሜዳ ለመመለስ የሚያስችላቸው ውሳኔ ላይ ድምጻቸውን ሰጥተዋል። ማህበራዊ ርቀታቸውን በጠበቀ መልኩ በአነስተኛ ቡድን ልምምድ እንዲያደርጉ ስምምነት ላይ ቢደረስም አሁንም ቢሆን መነካካት አልተፈቀደም።