ዛሬ ከሰዓት አስተናጋጇ ኡጋንዳን የገጠመችው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን 3 ለ 2 በማሸነፍ የዋንጫው ባለቤት ሆናለች።
የውድድሩ ዳኛ ለኢትዮጵያዋ ግብ ጠባቂ በስምንተኛው ደቂቃ ቀይ ካርድ ብታሳይም ቡድኗ በጎዶሎ ተጫዋች ድል ማምጣት ችላለች።
የመጀመሪያው አጋማሽ በኡጋንዳ 2-0 ቢጠናቀቅም በሁለተኛው አጋማሽ በረድዔት አስረሳኸኝ፣ በአርዬት ኦዶንግና በ82ኛው ደቂቃ በቱሪስት ለማ ጎሎች ኢትዮጵያ ባለድል መሆን ችላለች።