ጨረታው መስከረም 15 ኒውዮርክ ውስጥ የሚካሄድ ሲሆን ፤ ከሚገኘው ገንዘብ የተወሰነው በኒውዮርክ ለሚገኝ የማኅበረሰብ ፕሮጀክት ይውላልተብሏል። ቢጊ ዘውዱን አድርጎ ፎቶ የተነሳው ከመገደሉ (እአአ መጋቢት 9፣1997) ሦስት ቀን ቀደም ብሎ ነው ።ፎቶግራፉን ያነሳው ደግሞ ባሮን ክሌይቦርን የሚባል ባለሙያ ነው። በወቅቱ ራፐሩና ፎቶግራፉን ያነሳው ግለሰብ ዘውዱ ላይ ፈርመውበታል።ፎቶግራፈሩ ባሮን ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ዘውዱን እንደ ማስታወሻ ጠብቆ አቆይቶታል። ዘውዱ ከ200,000 እስከ 300 ሺህ ዶላር ድረስ ሊሸጥ እንደሚችል ተገምቷል።
የራፐር ቢአይጂ ዘውድ ለጨረታ ሊቀርብ ነው
previous post