ደቡብ አፍሪካዊው ኮሜዲያን ትሬቨር ኖዋህ የሚቀጥለውን ዓመት ግራሚ አዋርድ መድረክ እንደሚመራ የዝግጅቱ አስተባባሪዎች ይፋ አደረጉ።
በዚህም ትሬቨር ደስታውን ገልጿል።
‘’ምንም እንኳን በግራሚ ሽልማት ላይ እንድዘፍን ባይፈቀድልኝም ወይም በምርጥ የፖፕ አልበም ባልታጭም የዚህ ድንቅ ዝግጅት መድረክ እንድመራ መመረጤ አስደንቆናል’’ ብሏል ትሬቨር።
የሽልማቱ አዘጋጅ አካዳሚ ፕሬዝደንት ሃርቪ ሜሰን፤ መድረኩን ለመምራት ትሬቨር ምርጡ ‘አማራጭ’ ነው ብለዋል።