አዲሱ የጄምስ ቦንድ ፊልም ለዕይታ የሚበቃበት ቀን በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለሶስተኛ ጊዜ ተራዘመ።
ኖ ታይም ቱ ዳይ (No Time To Die) የተሰኘው ይህ ፊልም ከዚህ ቀደም ሁለት ጊዜ የተገፋ ሲሆን አሁን በመጪው ዓመት ጥቅምት ወር ላይ ለዕይታ እንደሚበቃ ከፊልሙ ድረ ገጽ ማወቅ ተችሏል።
ከዚህ ቀደም ለዕይታ ይበቃል ተብሎ የነበረው ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ላይ ነበር።
ፊልሙ ጄምስ ቦንድን በዓብይ ገጸ ባህሪነት በመሳል ለዓለም ሕዝብ ሲያስኮመኩም 25ኛው ሲሆን እንግሊዛዊው እና የብሪቴይን 007 የደህንነት ባለሙያ ወይንም ሰላይ ሆኖ የሚሰራው ዳንዔል ክሬግ ደግሞ ለመጨረሻ ጊዜ በፊልሙ ላይ መተወኑ ነበር።
በፊልሙ ላይ ሊያ ሴይዱክስ እና ራሚ ማሌክ ተሳትፈውበታል።