የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ያለ ኮከባቸው ሊዮኔል ሜሲ ኤልቼን ማሸነፍ ችለዋል ።
• ባርሴሎናን ከሜዳቸው ውጪ አሸናፊ ያደረገች ግብ ፍራንክ ዲ ዮንግ እና ሪኪ ፒዩግ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል ።
• ሰርጅዮ ቡስኬት በጨዋታ የቢጫ ካርድ መመልከቱን ተከትሎ ከ አትሌቲክ ቢልባኦ ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ የሚያመልጠው ይሆናል ።
• ፍራንክ ዲ ዪንግ በዘንድሮው የውድድር ዓመት አራት ጎሎችን አስቆጥሮ አራት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል ።
• ባርሴሎና ውጤቱን ተከትሎ በደረጃ ሰንጠረዡ ሶስተኛ ላይ ሲቀመጡ ከ ሪያል ማድሪድ በሶስት ነጥብ እንዲሁም ከመሪው አትሌቲኮ በሰባት ነጥቦች ርቀው ተቀምጠዋል ።
• ተጋጣሚያቸው ኤልቼ የዛሬውን ጨዋታ ጨምሮ ባለፉት አስራ ሶስት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻሉም ።