የአማዞኑ መስራች ጄፍ ቤዞስ ወደ ጠፈር በሚያደርጉት ጉዞ ለመብረር አንድ ግለሰብ 28 ሚሊዮን ዶላር በመክፈል የጉዞውን ጨረታ ማሸነፋቸው ተሰምቷል።
በያዝነው ሳምንት ቅዳሜ በነበረው የቢሊየነሩ ብሉ ኦሪጅን ኩባንያ አማካኝነት በተደረገው ጨረታ ነው የጠፈር በረራው አሸናፊ መሆናቸው የታወቁት።
የግለሰቡ ማንነት እስካሁን ባይታወቅም በሚቀጥሉት ሳምንታት ይፋ እንደሚሆን ተነግሯል።
ጨረታው ከ140 በላይ አገራት ዜጎች የተሳፉበት ነው ተብሏል።
በሐምሌ አጋማሽ ሊደረግ በተካሄደው በዚህ የጠፈር በረራ ላይ የጄፍ ቤዞስ ወንድም ማርክና ስማቸው ያልተጠቀሰ የጠፈር ቱሪስት ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሏል።