አሜሪካዊው ኮሜዲያን ቢል ኮዝቢ የፔንሲልቬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተወሰነበት ብይን እንዲሻር ከወሰነ ከሰዓታት በኋላ ከእሥር ተለቀቀ።
የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዳኞች ከዚህ በፊት በነበረው ፍርድ “የአካሄድ ጥሰት” አለ ሲሉ ተደምጠዋል። ነገር ግን ዳኞቹ ይህ ውሳኔያቸው ያልተለመደ መሆኑን አልካዱም።
የ83 ዓመቱ ኮዝቢ ከሶስት እስከ 10 ዓመት ድረስ ከርቸሌ እንዲከርም ተፈርዶበት እንደነበር አይዘነጋም።
ተዋናዩ ሁለቱን ዓመት እስር ፊላደልፊያ በሚገኝ ማረሚያ ቤት አሳልፏል።