የዩክሬን መከላከያ ሚኒስቴር ሴት የሰራዊቱ አባላት በሚቀጥለው ወር በሚደረገው ወታደራዊ ትዕይንት ከተለመደው የሰራዊቱ አልባሳት መለዮ ውጭ ከፍ ባለ ረዥም ተረከዝ (ሂል) ጫማ እንዲወጡ ለማድረግ ያቀደው ዕቅድ ቁጣን አስከትሏል።
በምክር ቤቱ የተቃዋሚዎች ፓርቲ ተወካይ ኢርያና ጌራሽቸንኮ እንዳሉት ይህ እኩልነት ሳይሆን ፆተኝነት ነው ብለውታል።
የቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት አባል የነበረችው ዩክሬን 30ኛ አመት የነፃነት ቀኗን በዓል ምክንያትም በማድረግ ለሚቀጥለው ወር ወታደራዊ ትዕይንት ያቀደችው።
የአገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ ጫማዎቹ የወታደራዊ መለዮ አካል ናቸው ብለዋል።
የሚኒስቴሩ ውሳኔ በርካታ ዩክሬናውያንን ያስደነገጠ ሲሆን ከምክር ቤት የተውጣጡ አባላትን የያዘ ቡድን መከላከያ ሚኒስትሩ አንድሪ ታራን ይፋዊ የሆነ ይቅርታ እንዲጠይቁ ጥሪ አቅርበዋል።