ቨርጂን ጋላክቲክ የተሰኘው ኩባንያ ባለቤት የሆኑት ሰር ሪቻርድ ብራንሰን ለንግድ አላማ ባስገነቧት ሮኬት የሚደረገው የመጀመሪያው ወደ ጠፈር የሚደረገው የቱሪስቶች ጉዞ በመጪው ሃምሌ 4 እንደሚሆን ቀን ቆርጠዋል።
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ጊዜ ወስዶ በአሜሪካ ውስጥ ሲገነባ በቆየው በዚህ ሮኬት አውሮፕላን ጀርባ ሰር ሪቻርድ ተሳፋሪ ይሆናሉ።
ሮኬቱ 90 ኪ.ሜ. ወይም ከባህር ወለል በላይ 295ሺህ ጫማ ከፍታ ላይ የመውጣት አቅም አለው።
ሰር ሪቻርድ የጠፈር በረራ አገልግሎትን ከሳይንሳዊ ምርምር ጉዞ ውጪ ለንግድ ዓላማ ማስተዋወቅ ፍላጎቴ ነው ካሉ ሰንብተዋል።
ወደ 600 የሚሆኑ ግለሰቦች ወደ ጠፈር ሄደው ለመጎብኘት ቀብድ ከፍለዋል።
የድርጅቱ ባለቤት በቅርቡ የሚደረጉት ይህ ጉዞም ደንበኞቹ ቀሪ የቲኬት ዋጋውን ለመክፈል እንደተቃረቡ ያመለክታል። የአንድ ቲኬት ዋጋም እስከ 250 ሺህ ዶላር ይደርሳል።