አውስትራሊያዊው የስፖርት ልብስ ድርጅት ልብሶቹ ‘ኮቪድ-19ን ይከላከላሉ፤ የወረርሽኙን ሥርጭትም ያስቆማሉ’ በማለቱ 3.6 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር [5 ሚሊየን የአውስትራሊያ ዶላር] ተቀጣ።
ይህ ማስታወቂያ የተሰራው በአውስትራሊያዊቷ የፋሽን ዲዛይነር ሎርና ጀን ነው።
ማስታወቂያው ልብሶቹ ‘ኤልጂ’ የተባለ አዲስ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተሰሩ መሆኑን ጠቅሶ ይህም እንደ ቫይረስና ባክቴሪያ ያሉ ማንኛውንም ረቂቅ ተህዋስያንን ይከላከላል ይላል።
በዚህም ድርጅቱ 3.6 ሚሊየን ዶላር ቅጣት እንዲከፍል የአገሪቷ ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላልፎበታል።