ሜሮን ሐደሮ ስመ ጥሩውን አኮ ኬይን የተባለው የአፍሪካ ስነ ፅሁፍ ሽልማትን በማሸነፍ የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ሁናለች።
” በፍፁም ደስተኛ ነኝ በድንጋጤ ውስጥ ነኝ – በራሱ መታጨቱ ትልቅ ክብር ነበር ስትል ለቢቢሲ ተናግራለች።
ያሸነፈችበት አጭር ፅሁፍ ጌቱ ስለተባለ አንድ ኢትዮጵያዊ ታዳጊ የሚተርክ ነው።
ታዳጊው በአዲስ አበባ የሚገኙ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና የውጭ ዕርዳታዎች ያላቸውን የሐይል ጫና ለማለፍ የሚያደርገውን ጥረት የሚያሳይ ነው።
ታሪኩ ዳኞችን ያስደነቃቸው ሲሆን እስከዛሬው ድረስ ከተለመደው ወጣ ባለ መልኩ የተፃፈ ነው ብለዋል።
ሜሮን በዚህ ሽልማት 13 ሺህ ዶላር አሸንፋለች።