አሜሪካዊው ቲክቶከር እና አንድ ጓደኛው በደቡባዊ ካሊፎርኒያ ሲኒማ ቤት በጥይት እንደተገደሉ ከፖሊስ እና ከሟች ቤተሰብ ተረጋግጧል።
በቲክቶክ በሚሠራው ቪዲዮ ዝናን ያተረፈውና አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ተከታዮች የነበሩት የ19 ዓመቱ አንቶኒ ባራጃስ እና የ18 ዓመቱ ራይሊ ጉድሪክሪች የተባለው ጓደኛው በኮሮና ግዛት በሚገኝ ሲኒማ ቤት ውስጥ ጭንቅላታቸው ላይ በተተኮሰባችው ጥይት ለህልፈት ተዳርገዋል።
ራይሊ ከጥቃቱ በኋላ ወዲያው የሞተ ሲሆን አንቶኒ ግን በሕይወት ቆይቶ የነፍስ ማዳን ክትትል ሲደረግለት ነበር። ሆኖም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሕይወቱ ማለፉን ቤተሰቡ አስታውቋል።