የአሜሪካ የዜና አውታር ሲኤንኤን የኮቪድ-19 ክትባት ሳይከተቡ ቢሮ የገቡ ሶስት ሰራተኞቹን ማሰናበቱን የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ኩባንያው አስገዳጅ የክትባቱን ህግ የጣሱ ሰራተኞቹን ሲያባርር የመጀመሪያው ኩባንያ ነው ተብሏል።
በአሜሪካ ውስጥ ያሉ ኩባንያዎች ሰራተኞቻቻውን እንዲከተቡ የመጠየቅ ህጋዊ መሰረት አላቸው።
ፌስቡክን እና ጉግልን ጨምሮ በርካታ ትልልቅ ኩባንያዎች በሚቀጥሉት ወራቶች ውስጥ ቢሮቻቸው ሙሉ በሙሉ ሲከፈቱ ሠራተኞቻቸው ተከትበው መምጣት አለባቸው ብሏል።