በኢትዮጵያ አንድ ቤተሰብ በትምህርት የደረሰበትን ጉዞ የሚያሳይ ፕሮጀክት የዘንድሮው ‘ኧርዝ ፎቶ’ ውድድር አሸናፊ ሆኗል።
ሮዚ ሃላም የተባለችው የፎቶ ባለሙያ በአንድ ፍሬም ላይ ሶስት ፎቶዎችን በማሳየት የመማር መብትን ታስቃኛለች።
በፎቶው ላይ የትምህርት መመዝገቢያ ዕድሜዋ ካለፈ በኋላ ትምህርት ቤት የገባችው ሰላማው በዋነኝነት ትታያለች።
ትምህርት ቤት በመግባት ለወላጆቿ መሰለችና ማርቆስ የመጀመሪያዋ ናት።
ቤተሰቡ ከእጅ ወደ አፍ በሆነ የግብርና ኑሮም ነው የሚተዳደሩት።
እነዚህ ፎቶዎች ‘ፒፕል’ (ሰዎች) በተሰኘው ዘርፍም አሸናፊ ሆነዋል።