አስራ አንድ የፓብሎ ፒካሶ የጥበብ ሥራዎች ላስ ቬጋስ በሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ ከተሰቀሉ ከ20 ዓመታት በኋላ 110 ሚሊዮን ዶላር ገደማ አውጥተው ተሸጡ።
ኤምጂኤም ሪዞርትስ የተባለው ኩባንያ ንብረት የሆኑትእነዚህ የጥበብ ሥራዎች ቤላጂዮ በተሰኘው ሆቴል ፒካሶ ሬስቶራንት ውስጥ ነበር ተሰቅለው የቆዩት።
የፒካሶን ሥራዎች በጨረታ በ110 ሚሊዮን ዶላር የሸጠው ኩባንያ በገንዘቡ ሌሎች የጥበብ ሥራዎችን እንደሚገዛ አስታውቋል።
ድርጅቱ ዘጠኝ የፒካሶ ሥዕሎችንና ሁለት የሴራሚክ ሥራዎችን ለጨረታ አቅርቦ ነው ለገዢዎች የሸጠው።