ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት መንግስት ያወጣውን ብሔራዊ የእንቅስቀሴ ገደብ ችላ ያለ አንድ ሩዋንዳዊ በአዞ ህይወቱ አልፎ መበላቱ ታወቀ።
ከቤት አትውጡ የሚለውን ትዕዛዝ ተላልፎ የወጣው ሩዋንዳዊ በአዞ ተበላ።
በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት መንግስት ያወጣውን ብሔራዊ የእንቅስቀሴ ገደብ ችላ ያለ አንድ ሩዋንዳዊ በአዞ ህይወቱ አልፎ መበላቱ ታወቀ።
ሩዋንዳ እና 12 ሚሊየን ህዝቧ የኮቪድ 19ኝን ስርጭት ለመግታት ሰዎች ከቤት እንዳይወጡ በመንግስት በተደነገገው መመሪያ ሥር ይገኛሉ።
ይህ ስሙ ያልተጠቀሰው ሩዋንዳዊ የአዞ ሰለባ ግን ናያብሮንጐ በተባለው ወንዝ ዓሳ በማጥመድ ላይ ሳለ ነበር አሳዛኙ አደጋ የተፈጠረው።