ፖርቹጋል ለሁሉም ስደተኞች እና ጥገኝነት ፈላጊዎች ሁሉ በጊዜያዊነት ሙሉ የዜግነት መብት በመስጠት፣ የኖቬል ኮሮና ቫይረስ ስርጭት እየሰፋ የመጣባትን የሃገሪቷን የጤና ጥበቃ ሙሉ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ ሙሉ መብት እንዲኖራቸው አድርጋለች።
ፖርቱጋል በአገሯ ለሚገኙ ጥገኝነት ጠያቂዎች በሙሉ የመኖሪያ ፈቃድ ልትሰጥ ነው።
ፖርቹጋል ለሁሉም ስደተኞች እና ጥገኝነት ፈላጊዎች ሁሉ በጊዜያዊነት ሙሉ የዜግነት መብት በመስጠት፣ የኖቬል ኮሮና ቫይረስ ስርጭት እየሰፋ የመጣባትን የሃገሪቷን የጤና ጥበቃ ሙሉ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ ሙሉ መብት እንዲኖራቸው አድርጋለች።
ይህ ውሳኔ በፖርቹጋል ኢሚግሬሽን ጉዳያቸው በእንጥልጥል የሚገኝ “የሁሉንም የውጭ ሃገራት ዜጐች መብቶችን ያለልዩነት ያስከብራል፤” ይህም ማለት ስደተኞቹ እስከ ጁን 30 ድረስ “በራሳቸው ብሔራዊ ክልል ውስጥ በቋሚ መደበኛ ነዋሪነት ሁኔታ ላይ” እንደሚገኙ ተደርጐ ይታሰባል፣ ሲሉ አርብ እለት የፖርቹጋሉ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስታውቋል።
ፖርቹጋሉ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጨምሮ እንዳብራራው ከሆነ፣ እዚህ ውሳኔ ላይ የተደረሰው፣ ለድንበር ጉዳይ አስፈፃሚዎች እንዲሁም ለስደተኞች እና ለጥገኝነት ፈላጊዎች በወቅቱ በስደተኞች ፅህፈት ቤት እየተሰራበት ያለውን የቀጠሮዎች የጊዜ ሰሌዳ በማይለውጥ ሁኔታ “የህዝብ ጤና አደጋዎችን ለመቀነስ” በሚል ነው።