የታይላንዱ ንጉስ ማሃ ቫጂራሎንግ ኮርን ወይም በሌላ መጠሪያቸው ራማ ኤክስ፣ ከአዲሱ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመሸሽ፣ በአልፐስ ተራሮች መካከል ባለችው ጋርሚሽ ፓርተንኪርቸን በተባለች የሪሶርት ከተማ ውስጥ በሚገኝ የቅንጦት ሆቴል ውስጥ ከ20 ወይዛዝርት አጀብ ጋር ራሳቸውን አግለዋል።
የታይላንዱ ንጉስ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት እራሳቸውን ከ20 ሴቶች ጋር አገለገሉ
የታይላንዱ ንጉስ ማሃ ቫጂራሎንግ ኮርን ወይም በሌላ መጠሪያቸው ራማ ኤክስ፣ ከአዲሱ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመሸሽ፣ በአልፐስ ተራሮች መካከል ባለችው ጋርሚሽ ፓርተንኪርቸን በተባለች የሪሶርት ከተማ ውስጥ በሚገኝ የቅንጦት ሆቴል ውስጥ ከ20 ወይዛዝርት አጀብ ጋር ራሳቸውን አግለዋል።
በመገናኛ ብዙሃን ዘገባ መሠረት፣ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የተነሳ በክልሉ የሚገኙ ሆቴሎች እና የእንግዳ ማረፊያዎች (ገስትሀውሶች) የተዘጉ ይሁን እንጂ፣ እኚህ የ67 አመት ንጉስ ሶነንቢችል የተባለውን ግራንድ ሆቴል ሙሉ በሙሉ በመያዝ 20 ቆነጃጅትንና ብዙ ሰራተኞቻቸውን አስከትለው ለብቻቸው ከትመዋል። ከክልሉ ምክር ቤት የተላለፈውን “ልዩ ፈቃድ” ተከትሎ፣ የቅንጦት ሆቴሉ ንጉሱን እና አጀባቸውን ተቀብሎ ማስተናገድ ጀምሯል። ዘገባዎቹ እንደገለፁት ከሆነ፣ አራቱ የንጉሱ ሚስቶች አብረዋቸው በሆቴሉ ውስጥ መኖር ያለመኖራቸው በግልፅ አልታወቀም።