የድመቱ ቅርጽ ይተገኘበት ስፍራ በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ተብሎ የተመዘገበ ቦታ ሲሆን በርካታ የመሬት ላይ ቅርሶችን የያዘ ቦታ ነው። ቅርሶቹም እስከ 2000 ዓመታት ድረስ ያስቆጠሩ ናቸው።
ተመራማሪዎች እንደገለጹት ይህ ትልቅ የድመት ቅርስ በከፍታ ቦታው ላይ የተሰራው ደማቅ ቀለም ያለውን የበረሃ አፈር በመጠቀም ነው።የድመቱ ቅርጽም እስከዛሬ ድረስ ሳይታወቅ ቆይቷል። በቅርቡ ግን በከፍታ ቦታው ላይ የምርምር ቦታ ለማቋቋም በማሰብ መንገድ ለመስራት ሲሞከር ነው ግዙፉ የድመት ቅርጽ የተገኘው።
በከፍታ ቦታው ላይ ጋደም ያለው ድመት ቅርጽ አካባቢው ለመጎብኘት ለሚመጡ ሰዎች ምቹ ቦታ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል።