በማልታ ሊግ የደመቀችው ሎዛ አበራ የአሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛውን ኢትዮጲያ ንግድ ባንክን ለመቀላቀል ተስማምታለች፡፡
ሴናፍ ዋቁማን ከአዳማ ከተማ ለማስፈረም በተደረገው ትንቅንቅ በመከላከያ ተረተው እጅ የሰጡት ኢትዮጲያ ንግድ ባንኮች በሎዛ ከመከላከያ የገጠማቸውን ትግል አሸንፈው በእጃቸው ያስገቡ ሲሆን ልደታ ቤ/ክ አካባቢ በሚገኘው ዛጉኤል ህንጻ ላይ ባለው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከቀኑ 10 ሰአት ላይ በሚኖረው የፊርማ ስነስርአት በይፋ ይገለጻል ተብሎ ይጠበቃል፡
እስከ 90ሺ ብር ወርሃዊ ደሞዝ ሊከፈላት የሚችለው ሎዛ በኢትዮጲያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ትደምቃለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡