የ2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መክፈቻ ጨዋታ ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲጀመር ድሬዳዋ ከተማ ከሰበታ ከተማ 0ለ0 ተለያይተዋል።
የፕሪሚየር ሊጉ የዛሬ ሁለተኛ ጨዋታ 9:00 ሰዓት ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከፋሲል ከነማ ጋር እንደሚጫወቱ የወጣው መርሐ ግብር ያስረዳል።
የሊጉ መርሐ ግብር ነገ እና ከነገ በስቲያ ሲቀጥል እሁድ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ኢትዮጵያ ቡና ከወልቂጤ ከተማ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ ደግሞ ጅማ ከተማ ከአዳማ ከተማ ጋር ይጫወታሉ።
የፊታችን ሰኞ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ላይ ወላይታ ድቻ ከሀዲያ ሆሳዕና እንዲሁም 9:00 ሰዓት ላይ ባህር ዳር ከተማ ከሲዳማ ቡና ጋር እንደሚጫወቱ ይጠበቃል።
ሁሉም ጨዋታዎች በአዲስ አበበ ስታዲየም የሚካሄዱ ይሆናል።