• የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ተከታታይ ድል በማስመዝገብ በ ሜሲ እና ግሪዝማን ግቦች አትሌቲክ ቢልባኦን 2 ለ 1 አሸንፈዋል ።
• ባርሴሎና የምሽቱን ድል ተከትሎ በላሊጋው አምስተኛ ተከታታይ ድላቸው ሆኗል ።
• ባርሴሎና ሪያል ማድሪድ በመብለጥ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጡ ከመሪው አትሌቲኮ ማድሪድ በአስር ነጥብ ርቀዋል ።
• የምሽቱን ጎል ተከትሎ ሜሲ በባርሴሎና ቤት 650ኛ ጎሉን ከመረብ አሳርፏል ።
• ግሪዝማን ከ አዲሱ የፈረንጆች ዓመት በኋላ ወደ ቀደመ አቋመ ሲመለስ በሰባት ጨዋታዎች አምስት ጎሎችም አስቆጥሮ ሶስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል ።
• ቶተንሀም ተከታትይ ሽንፈትን ሲያስተናግዱ ምሽቱን በ ትሮሳርድ ብቸኛ ግብ በ ብራይተን ተሸንፈዋል ።
• ብራይተን በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያውን ድል በሜዳቸው ማሳካት ችለዋል ።
• ስፐርስ ባለፉት አስር የሊጉ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻሉት በሶስቱ ሲሆን በአራት ጨዋታዎች ላይ ሽንፈት ቀምሰዋል ።
- የባርሴሎና የጨዋታ ጎሎች ከላይ በቪድዮው ላይ ተያይዟል ።