በ ክረምቱ ከ ካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ተገፍቶ የወጣው ዩራጋዊው የፊት መስመር አጥቂ ሉዊስ ሱዋሬዝ በላሊጋው መሪ አትሌቲኮ ማደሪድ ደማቅ ጊዜን እያሳለፈ ይገኛል ።
ሉዊስ ሱዋሬዝ ሰፊ ሀሳቦችን ሲያነሳ በተለይም ከ ባርሴሎና ጋር የተለያየበትን መንገድ ተናግሮ አልፏል ።
” በ ባርሳ ልምምድ እንዳልሰራ ነግረውኝ ነበር ፣ ነገር ግን ኮንትራት እስካለኝ ድረስ ልምምድ መስራቴን እንደማላቆም ነገርኳቸው ።
ክለቡ ምንም ዓይነት ማብራሪያ አልሰጠኝም ፣ ይህ ውሳኔ የአዲሱ አሰልጣኝ ሮናልድ ኩማን ብቻ እንደሆነ ነግረውኛል ” ሲል ወቅቱን በማስታወስ አስተያየቱን ሰጥቷል ።