የለንደኑ ክለብ ቼልሲ በቶማስ ቱሄል ስር ባለመሸነፍ ጉዟቸው ሲቀጥሉ በ ለንደን ደርቢ በ ጆርጂንሆ ብቸኛ ግብ ቶተንሀምን ማሸነፍ ችለዋል ።
• ጆርጂንሆ በ ፍፁም ቅጣት ምት ማስቆጠር ሲችል በቼልሲ ቤት በሊጉ ካገኛቸው አስር ፍፁም ቅጣት ስምንቱን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል ።
• የቼልሲ የ አካዳሚ ፍሬዎች ዳግም በ ቱሄል ስር ሲያብቡ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ሀድሰን ኦዶይ እና ማውንት የጨዋታው ኮከብ በመባል ተመርጠዋል ።
• ቶተንሀም የምሽቱን ሽንፈት ተከትሎ ከመሪው ሲቲ በአስራ አራት ነጥቦች ርቀው ተቀምጠዋል ።
• ጆዜ ሞሪንሆ በአሰልጣኝነት ዘመናቸው በሜዳቸው በተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት ገጥሟቸዋል ።
• ቼልሲ በ ቶማስ ቱሄል እየተመሩ አንድም ግብ ሳይቆጠርባቸው መጓዛቸውን ቀጥለዋል ።