• ቼልሲ በ ኤ ፌ ካፑ ባርንስሌይን በታሚ አብርሀም ብቸኛ ጎል በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፋቸውን አረጋግጠዋል ።
• ቶማስ ቱሄል ቼልሲን ከተረከቡ በኋላ አንድም ሽንፈት ያልቀመሱ ሲሆን ስድስት ጎሎችን አስቆጥረው አንድ ግብ ብቻ አስተናግደዋል ።
• ባየር ሙኒክ በ ቤንጃሚን ፓቫርድ ብቸኛ ግብ ታይገርስን በማሸነፍ የአለም የክለቦች ዋንጫን ማሸነፍ ችለዋል ።
• ሀንስ ፍሊክ ሌላ ዋንጫ ማሳካት ሲችሉ በ 68 ጨዋታዎች ስድስተኛው ዋንጫቸው ሆኗል ።
• ታሚ አብርሀም በዘንድሮው የውድድር ዓመት 1425 ደቂቃዎችን ተሰልፎ መጫወት ሲችል አስራ ሁለት ጎሎችን አስቆጥሮ ስድስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል ።
• ባየር ሙኒክ ከ ባርሴሎና በመቀጠል ስድስት ዋንጫዎችን ከፍ ማድረግ የቻሉ ሁለተኛው ክለብ ሆነዋል ።