• ማንችስተር ሲቲ ከ ከተማ ተቀናቃኛቸው ዩናይትድ በ አስራ ሁለት ነጥብ ርቀው ተቀምጠዋል ።
• የአምናው የሊጉ ሻምፒዮን ሊቨርፑል ከወዲሁ ከ ሊጉ መሪ ሲቲ በ አስራ ዘጠኝ ነጥቦች አንሰዋል ።
• የላሊጋው መሪ አትሌቲኮ ማድሪድ ቀሪ አንድ ጨዋታ እየቀራቸው ሊጉን በ አምስት ነጥብ ርቀት ይመራሉ ።
• ኤይባር ፣ ቫላዶሊድ ፣ አላቬስ ፣ ኤልቼ እና ሁሴካ በወራጅ ቀጠናው በሁለት ነጥብ ብቻ ተራርቀው ተፋጠዋል ።
• ኢንተር ሚላን በሴርያው መሪነት ሲቀመጡ በ ሳምንቱ ነጥብ የጣሉት ጁቬንቱስ በአስር ነጥቦች ርቀዋል ።
• በጀርመን ቡንደስሊጋ የአምናው ሻምፒዮን ባየር ሙኒክ ከ ተከታያቸው ሌፕዚግ በሁለት ነጥብ ልዩነት ርቀው አንገት ለ አንገት ተናንቀዋል ።