ቼልሲ በቶማስ ቱሄል እየተመሩ ኤቨርተንን በማሸነፍ ወደ ” TOP FOUR ” የሚያደርጉትን ግስጋሴ አሳምረዋል ።
• ቼልሲ ባለፉት አምስት ጨዋታዎች ግብ ሳይቆጠርባቸው በመውጣት አዲስ ታሪክ አስመዘግበዋል ።
• ጆርጂንሆ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ሰባተኛ ጎሉን ሲያስቆጥር ሁሉም ጎሎች በፍፁም ቅጣት ምት የተቆጠሩ ናቸው ።
• ቼልሲ የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ከአምናው የሊጉ ሻምፒዮን ሊቨርፑል በሰባት ነጥብ ለመራቅ ችለዋል ።
• ሴዛር አዝቢልኬታ በቶማስ ቱሄል ስር ሁሉንም ጨዋታዎች በቋሚ አሰላለፍ የጀመረ ቀዳሚው ተጫዋች ሆኗል ።
• ቼልሲ በቶማስ ቱሄል ስር በሜዳቸው አንድም ግብ አላስተናገዱም ።