በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ትናንት ምሽት ሁለት ጨዋታዎች ተካሄደዋል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ ቦሩሲያ ሞንቼግላድባህን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ባሸነፈበት ጨዋታ፥ ኬቪን ደብሩይነ እና ኢካይ ጉንዶኻን የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡
በደርሶ መልስ ውጤት ማንቼስተር ሲቲ 4 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል፡፡
በሌላ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ አታላንታን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
ካሪም ቤንዜማ፣ ሰርጂዮ ራሞስ እና ማርኮ አሴንሲዮ የማሸናፊያ ጎሎቹን ለሪያል ማድሪድ ሲያስቆጥሩ፥ ሙሪዬል ደግሞ ለአታላንታ የማስተዛዘኛ ጎሏን ማስቆጠር ችሏል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ሪያል ማድሪድ በደርሶ መልስ ውጤት 4 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሩብ ፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
ፒ ኤስ ጂ፣ ቦሩሲያ ዶርትመንድ፣ ሊቨርፑል እና ፖርቶ ቀደም ብለው ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡