የ ኦሊ ጎነር ሶልሻየር ስብስብ በ ኢህናቾ እና ዩሪ ቴሌምናስ በተቆጠሩባቸው ጎሎች በሌስተር ሲቲ ተሸንፈዋል ።
ኢህናቾ ባለፉት ዘጠኝ በሁሉም የውድድር መድረክ ባደረጋቸው ጨዋታዎች ዘጠኝ ግቦችን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል ።
ስዊድናዊው የቀያይ ሴጣኖቹ የመሐል ተከላካይ ቪክቶር ሊንድሎፍ በማንችስተር መለያ 150ኛ ጨዋታውን አድርጓል ።
ሌስተር ሲቲ በውድድር መድረኩ ለግማሽ ፍፃሜ ሲያልፉ ከ ሰላሳ ዘጠኝ አመት በኋላ ነው ።
ሌስተር ሲቲ በቀጣይ በግማሽ ፍፃሜው ከ ሳውዝሀምፕተን ጋር የሚጫወቱ ይሆናል ።