• ጊኒ እና ቡርኪና ፋሶ በዛሬው ዕለት ለ ካሜሮን የ 2021 አፍሪካ ዋንጫ ማለፋቸው አረጋግጠዋል ።
• የቼልሲው የመስመር ተጫዋች ክርስቲያን ፑሊሲች በመጪው የቶክዮ ኦሎምፒክ ለሀገሩ አሜሪካ ተሰልፎ መጫወት እንደሚፈልግ አሳውቋል ።
• ማርቲን ኦዴጋርድ በመድፈኞቹ ቤት የመቆየት ፍላጎት መኖሩን ተከትሎ በቀጣይ በአርሴናል መለያ የመታየት እድል እንዳለው ተጠቁሟል ።
• ብራዚላዊው የፒኤስጂ የፊት መስመር ተጫዋች ኔይማር ኮንትራቱን ለማራዘም ከጫፍ መድረሱ ይፋ ሆኗል ።
• የሴርያው ክለብ ጁቬንቱስ ምክትል ፕሬዝዳንት ፓቬል ኔድቬድ ኮከባቸው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በክለቡ እንደሚቆይ ማረጋገጫ ሰጥቷል ።
• ኔድቬድ ከ ሮናልዶ በተጨማሪም አሰልጣኝ አንድርያ ፒርሎ በቀጣይ ዓመትም ቡድኑን በሀላፊነት እንደሚመራ ይፋ አድርጓል ።