አታላንታ በ ሉካስ ሙሪየል ሁለት ጎሎች እና ዱቫን ዛፓታ አንድ ግብ ዩዲኒዜን 3 ለ 2 ማሸነፍ ችለዋል ።
ሙሪያል በውድድር ዓመቱ አስራ ስምንት ጎሎችን ሲያስቆጥር ከ ሉካኩ እና ሮናልዶ ብቻ ተብልጦ ይገኛል ።
ላዚዮ በመጨረሻው ደቂቃ ካይሲዶ ያስቆጠራት ግብ ነጥብ ከመጣል ስትታደጋቸው አዲስ አዳጊዎቹን ስፔዚያን 2 ለ 1 አሸንፈዋል ።
የስፔዚያን አቻ ያደረገች ግብ ያስቆጠረው ዳንኤል ቬርዲ ድንቅ የመቀስ ምት ከመረብ ማሳረፍ ችሏል ።
ሰባት ጎሎች በተቆጠሩበት መርሐ ግብር ናፖሊ በ ኢንሲኔ ፣ ኦሲሜን ፣ ሜርትንስ እና ሎሬንዞ ግቦች 4 ለ 3 ክሮቶኔን ማሸነፍ ችለዋል ።
በሌላ የሴርያው መርሐ ግብር ሳሱሎ እና ሮማ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት መለያየት ችለዋል ።
በዛሬው ዕለት የተመዘገቡትን ውጤየ ተከትሎ ጁቬንቱስ ከደረጃ ሰንጠረዡ አራት ውስጥ ውጪ ሆነዋል ።
ጁቬንቱስ በደረጃ ሰንጠረዡ አምስተኛ ላይ ሲቀመጡ ከሰዓታት በኋላ በቱሪን ደርቢ ከ ቶሪኖ ጋር ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ ።