ሪያል ማድሪድ በ ኤል ክላሲኮው ባርሴሎናን 2 ለ 1 በማሸነፍ ደረጃቸውን ያሻሻሉበት ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል ።
• ቤንዜማ በላሊጋው አስራ ዘጠነኛ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል ።
• ሜሲ ባርሴሎና በ ኤል ክላሲኮው ባስቆጠሩት ባለፉት አስራ ሁለት ጎሎች ላይ ምንም ተሳትፎን ማድረግ ሳይችል ቀርቷል ።
• ሪያል ማድሪድ በሁለት ጎሎች እየመሩ ለዕረፍት ሲወጡ ከ አስራ ሶስት ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ።
• ባርሴሎና በ ኤል ክላሲኮ በእድሜ ትንሽ የሆነ ቡድን ይዘው ሲቀርቡ ከ አስራ ስድስት ዓመታት በኋላ ሆኖ ተመዝግቧል ።
• ቶኒ ክሩስ በእግር ኳስ ህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በ ባርሴሎና ላይ ግብ ማስቆጠር ችሏል ።
• ካሪም ቤንዜማ ባለፉት ሰባት የላሊጋ ጨዋታዎች በሙሉ ግብ አስቆጥሯል ።
• ናቾ የቢጫ ካርድ መመልከቱን ተከትሎ ቀጣይ በ ላሊጋው ሄታፌን ሲገጥሙ የማይሰለፍ ይሆናል ።
• ባርሴሎናዎች በውድድር ዓመቱ ባደረጉት የ ኤል ክላሲኮ ጨዋታዎች በ ላሊጋው ሽንፈት ገጥሞቸዋል ።