• በመጪው ክረምት ከ አሰልጣኛቸው ሀንስ ፍሊክ ጋር እንደሚለያዩ የሚጠበቁት ሙኒኮች በ ሜንዝ 2 ለ 1 ተሸንፈዋል ።
• ሙኒክ ሽንፈት ማስተናገዳቸውን ተከትሎ የ ቡንደስሊጋ አሸናፊ መሆናቸው ለማረጋገጥ የነበራቸውን እድል ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል ።
• ሌፕዚግ በነገው ዕለት በ ስቱትጋርት የሚሸነፉ ከሆኑ ሙኒክ ሻምፒዮን የሚሆኑ ይሆናል ።
• ኤርሊንግ ሀላንድ አዲስ ታሪክ ሲፅፍ ከ 21 ዓመት በፊት 38 ጎሎችን በ ቡንደስሊጋው ማስቆጠር የቻለ ቀዳሚው ተጫዋች ሆኗል ።
• ሀላንድ በዘንድሮው የውድድር ዓመት በ ቡንደስሊጋው በ ሀያ ስድስት ጨዋታዎች ሀያ አምስት ጎሎችን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል ።
• ሮበርት ሊዋንዶውስኪ በውድድር ዓመቱ በ ሀያ ስድስት ጨዋታዎች ሰላሳ ስድስት ጎሎችን አስቆጥሯል ።