ቀያይ ሴጣኖቹ ከመመራት ተነስተው ሮማን 6 ለ 2 ሲያሸንፉ ወደ ስፔን ያቀኑት መድፈኞቹ በ ቪያሪያል 2 ለ 1 ተሸንፈዋል ።
• ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ለቀያይ ሴጣኖቹ በሁለም የውድድር መድረኮች በ አርባ አንድ ጎሎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ማድረግ ችሏል ።
• ብሩኖ ፈርናንዴዝ ሀያ አንድ የፍፁም ቅጣት ምቶችን ሲያገኝ የሳተው አንዱን ብቻ ነው ።
• ካቫኒ ካለፉት አምስት ጨዋታዎች መካካል በአምስቱ ግብ አስቆጥሯል ።
• ኤዲን ዜኮ ከ ማንችስተር ዩናይትድ ጋር ባደረገው አስር ጨዋታዎች ስምንተኛ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል ።
• ካቫኒ በሮማ ላይ በድምሩ ያስቆጠራቸውን የግብ መጠን ወደ ዘጠኝ ከፍ አድርጎታል ።
• ዜኮ ካስቆጠራቸው ስምንት ጎሎች መካከል ስድስቱ በ ኦልድ ትራፎርድ ያስቆጠረው ናቸው ።
• ብሩኖ ፈርናንዴዝ በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ መጠን ወደ ሀያ ስድስት ከፍ አድርጎታል ።
• ብሩኖ ፈርናንዴዝ በተከታታይ ሶስት የውድድር ዓመታት ሀያ አምስት እና ከዚያ በላይ ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል ።
• አርሴናል ዳኒ ሴባዮስን በሁለተኛው አጋማሽ በቀይ ካርድ አጥተዋል ።