ፈረንሳዊው የቼልሲ ድንቅ የመሐል ሜዳ ተጫዋች ንጎሎ ካንቴ ከጣፋጩ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ማግስት አስተያየቱን ሰጥቷል ።
“ በልጅነቴ በ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ባሉበት ትልልቅ ስታዲየሞች ውስጥ እራሴን አገኛለው ብዬ አላስብም ነበር ።
ግን ዛሬ ላይ እዚህ ለመድረስ ችያለው ፣ ከ አስር ዓመታት በፊት የሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታን በቴሌቪዥን ተመልክቻለሁ ፣ ዛሬ ላይ ግን ቡድኔ እንዲያሸንፍ እያገዙኩኝ ነው ” ሲል ንጎሎ ካንቴ ተናግሯል ።