በ ኮከቧ ማሪክ ሀምሲክ አምበልነት የምትመራው ስሎቫኪያ ሼዝኒ በራሱ ላይ እንዲሁም በ ሚላን ስክሪናር ጎል ፖላንድን 2 ለ 1 በማሸነፍ ውድድሯን በድል ጀምራለች ።
• የፖላንድ ግብ ጠባቂ ሼዝኒ በአውሮፓ ዋንጫው ላይ ራሱ ላይ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ግብ ጠባቂ ሆኗል ።
• ፖላንዳዊው ክሪኮውያክ በዘንድሮው የአውሮፓ ዋንጫ የመጀመሪያውን የቀይ ካርድ የተመለከተ ተጫዋች ሆኗል ።
• የስሎቫኪያው ብሔራዊ ቡድን አምበል ማሪክ ሀምሲክ 127ኛ ጨዋታውን ለሀገሩ ማድረግ ችሏል ።
• ሚላን ስክሪናር ለ ስሎቫኪያ ብሔራዊ ቡድን ሶስተኛ ጎሉን በድምሩ ከመረብ አሳርፏል ።