የአለም ዋንጫ የፍፃሜ ተፋላሚዋ ክሮሽያ ከደካማ የአውሮፓ ዋንጫ ጅማሮ በማንሰራራት ስኮትላንድን በማሸነፍ ወደ ቀጣዪ ዙር ማለፋቸውን አረጋግጠዋል ።
• ሞድሪች ፣ ቭላሲች እና ፔርሲች የ ክሮሽያን የማሸነፊያ ጎሎች ያስቆጠፉ ተጫዋቾች ናቸው ።
• በምድቡ የምትገኘው እንግሊዝ በ ስተርሊንግ ብቸኛ ግብ በማሸነፍ የምድቡ አንደኛ በመሆን ቀጣዩን ዙር ተቀላቅለዋል ።
• ጀዳን ሳንቾ ተቀይሮ በመግባት በአውሮፓ ዋንጫው የመጀመሪያ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል ።
• ሉካ ሞድሪች በአውሮፓ ዋንጫው ለክሮሽያ ግብ ማስቆጠር የቻለ በእድሜ አንጋፋው እና ትንሹ ተጫዋች ሆኗል ።
• እንግሊዝ ከ ጣልያን በመቀጠል በምድብ ጨዋታዎች አንድም ግብ ያልተቆጠረባት ሀገር ሆናለች ።