ባለፈው ዓመት ግንቦት ሚኒሶታ ውስጥ አፍሪካ አሜሪካዊውን ጆርጅ ፍሎይድን በመግደል ወንጀል የተከሰሰው አሜሪካዊው ነጭ የቀድሞ የፖሊስ መኮንን 22 ዓመት ከስድስት ወር እስር ተፈረደበት።
የዴሪክ ቻውቪን ቅጣት “የተጣለበትን እምነት እና ኃላፊነት በማጉደል እንዲሁም በታየው ልዩ ጭካኔ” ላይ የተመሠረተ መሆኑን ዳኛው ተናግረዋል።
የ48 ዓመቱ ጆርጅ ፍሎይድ ህይወት ያለፈው ቻውቪን አንገቱ ላይ ለዘጠኝ ደቂቃዎች የህል ተንበርክኮ ተንፋሽ አሳጥቶት ከቆየ በኋላ ነበር።
ግድያው ዘረኝነትን እና የፖሊስ ጭካኔን ሚቃወሙ ዓለም አቀፍ ተቃውሞዎችን አስከትሏል።