ወርልድ ፉትቦል ማስተር ኢትዮጵያ የጠራው ጋዜጣዊ መግለጫ በአሁን ሰዓት እየተካሄደ ሲገኝ በመጪው ህዳር 16/2014 ሰላም እና ቱሪዝም በሚል መሪ ቃል በ ” BRAZIL ALL STARS ” እና በ ” AFRICA ALL STARS ” መካከል በ አዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታ እንደሚኖር አሳውቋል ።
የ ” Love To Nation መስራች እና ፕሬዝዳንት የሆኑት ማስተር ሄኖክ መገርሳ በ መግለጫው እንደተናገሩት አርባ ሁለት ኮከቦች ለዚህ ዝግጅት እንደሚመጡ ገልፀዋል ።
ከ እነዚህም መካከል ሪካርዶ ካካ ፣ ዱንጋ ፣ ሮናልዲንሆ ፣ ሳሙኤል ኤቶ ፣ ዲድየር ድሮግባ እና ሌሎችም ስመ ጥር ተጫዋቾች እንደሚመጡ ይጠበቃል ።