የ ቶኪዮ ኦሎምፒክ በ ደማቅ ሁኔታ መካሄዱን ሲቀጥል ያልተጠበቀ ክስተቶችን በማሳየት ላይ ይገኛል ።
• በ 100 ሜትር የ ወንዶች የፍፃሜ ውድድር ጣልያናዊው ማርሴል ጃኮብስ የ ግሉን ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ የ አለማችን ፈጣኑ ሰው መሆኑን አሳይቷል ።
• በ ከፍታ ዝላይ 2.37 ከፍታን መዝለል የቻሉት ኳታራዊው ሟታዝ ባርሽም እና ጣልያናዊው ጂያንማርኮ ታምቤሪ የ ወርቅ ሜዳሊያውን ለመጋራት ችለዋል ።
• ሁለቱ አትሌቶች ሁሉንም የ ከፍታ ዝላይ ተመሳሳይ ውጤት ማስመዝገባቸውን ተከትሎ አትሌቶቹ ባደረጉት ምክክር የ ወርቅ ሜዳሊያውን ለመጋራት መርጠዋል ።
• ሟታዝ ባርሻም በ ለንደን ነሐስ እንዲሁም በ ሪዮ ኦሎምፒክ የ ብር ሜዳሊያ ካገኘ በኋላ ዘንድሮ ላይ የመጀመሪያ ወርቁን በ ውድድሩ ማሳካት ችሏል ።