ያለ ኮከባቸው ሊዮኔል ሜሲ የ መጀመሪያ የ ላሊጋ ጨዋታቸውን ያካሄዱት ባርሴሎናዎች 4 ለ 2 በሆነ ውጤት ሪያል ሶሴዳድን አሸንፈዋል ።
• ማርቲን ብራትዌት ሁለት እንዲሁም ጄራርድ ፒኬ እና ሰርጂ ሮቤርቶ የ ግቦቹ ባለቤት ናቸው ።
• የ ላሊጋውን ከፍተኛ ግብ አግቢነት ቤንዜማ ፣ ኮሬራ እና ብራትዌት በ እኩል ሁለት ጎሎች እየመሩ ይገኛሉ ።
• ኦርያዛባል እና ሎቤቴ የ ሶሴዳድን የ ማስተዛዘኛ ጎሎች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው ።
• የ ባርሴሎናን ቀዳሚ ጎል ያስቆጠረው ፒኬ በተከላካይ ስፍራ የ ክለቡ ሁለተኛ ከፍተኛ ግብ አግቢ መሆን ችሏል ።
• አዲስ ፈራሚው ሜምፊስ ዴፓይ በ ጨዋታው ለ ግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል ።
• አንቱዋን ግሪዝማን በ ባርሴሎና መለያ 100ኛ ጨዋታውን አድርጓል ።